Sunday, February 15, 2015

አቶ ያሬድ አደመ በደረቅ ቼክ ማጭበርበር ታሰረ


አንድ አድርገን የካቲት 9 2007 ዓ.ም

በአዋሳ ገብርኤል እና በደቡብ ኢትዮጵያ የተፈጠረውን የተሐድሶ እንቅስቃሴ በግምባር ቀደምነት ጠፍጥፎ በመፍጠር የሚታወቀው ከዚያም አልፎ ከአገር ውጭም በተለይ በዱባይ ከመሰሎቹ ጋር በመሆን ከሊቀጳጳሱ እውቅና ውጭ በአዳራሽ ቤተ ክርስቲያን በመክፈት የሚታወቀው የተሐድሶያውን ፊት አውራሪ አቶ ያሬድ አደመ ባደረገው የደረቅ ቼክ ማጭበርበር ጉዳይ አቃቂ ቂሊንጦ እስር ቤት ወርዷል ። በጉዳዩም ላይ በመቀጠል በጋሻው ደሳለኝ አሸናፊ ገብረማርያም እና ሌሎች ሁለት ለጊዜው ስማቸው ያልተጠቀሱ ሰዎች ከጉዳዩ ጋር ተያያዥነት ባለው ጉዳይ ይጠየቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡


አቶ ያሬድ ከዚህ ቀደም " መዝሙረ ተዋሕዶ " በሚል ርእስ የዘማርያንን የመዝሙር መጽሐፍ በማሳተም ለደራስያኑም ሆነ ለዘማርያኑ ምንም አይነት ክፍያ ሳይፈጽም ላባቸውን ሜዳ እንዳስቀረ ይታወቃል ይህ ሰው ከቤተ ክርስቲያኗ እና ከቅዱስ ሲኖዶስ እውቅና ውጪ በመናፍቃን ግልፅ የሆነ የማያቋርጥ ድጋፍ የሚንቀሳቀሰውን እና በየሳምንቱ እሁድ እሁድ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ " ታኦሎጎስ " የተሰኘ የተሐድሶ ፕሮግራም የሚተላለፍበትን ድርጅት አቶ በጋሻው ደሳለኝ እና ከበሪሁን ጋር በሽርክና የሚያንቀሳቅስ ሲሆን የቴሌቪዥን ፕሮግራሙ ፈቃድም  በበሪሁን ስም መሆኑም ይታወቃል

ከዚህ ቀደም የአርቲስት አቦነሽ መዝሙር በራስ አምባ ሆቴል በተደረገው የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ አንድ ሲዲ ከመቶ ሺህ ብር በላይ በጨረታ የሸጡ ሲሆን አሁን በአርቲስቷ ስም ብዙ ብር በማግበስበስ ኪሳቸውን ከሞሉ በኋላ ለአቦነሽካሴትሽ አልተሸጠም› እንዳሏት ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሰዎች ይናገራሉ፡፡


በኢትዮጵያ ወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ደረቅ ቼክ ማጭበርበር ከሦስት ዓመት በላይ ለሚሆን ጊዜ ዘብጥያ እንደሚያወርድ ይታወቃል

7 comments:

  1. ሰዉ የዘራዉን ያንኑ ያጭዳል አቶ ያሬድ አደመ በደረቅ ቼክ ማጭበርበር ታሰረ ፡፡

    ReplyDelete
  2. Egziabeher lehulum ende seraw yekefelewal

    ReplyDelete
  3. እስከ ዛሬ በሙስና የተሰበሰበው ገንዘብ በነጻ ያወጣዋል

    ReplyDelete
  4. egna zimenibel Egiziabiher yinager

    ReplyDelete
  5. Enante weregnoch Yared Ademe be nesa telekeke

    ReplyDelete