Friday, December 5, 2014

ጌርጌሴኖን የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማኅበር

አንድ አድርገን ኅዳር 27 2007 ዓ.ም

  • ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል  በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል፡፡” ምሳሌ 1917
ጌርጌሴኖን የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማኅበር ከስምንት ዓመታት በፊት በአቶ መለሰ አማካኝነት የአእምሮ ህሙማንን ለመርዳት የተቋቋመ ማኅበር ነው፡፡ ማኅበሩ ከተቋቋበት ጊዜ አንስቶ በተለያየ ችግር ጎዳና ወድቀው የነበሩ ሰዎችን በማንሳት ሲረዳ ቆይቷል፡፡ ባሳለፍነው ዓመት ውስጥ ጌርጌሴኖን የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማኅበርን ከሦስት ጊዜ በላይ ሄደን መጎብኝት ችለን ነበር ፡፡ እኛ ቦታው ላይ ደርሰን የተመለከትናቸው ራሳቸውን የማያውቁ ፤ እናት ፤ አባት ፤ እህት ፤ ወንድም ፤ ዘመድና የእኔ የሚሉት ሰው የሌላቸው በአእምሮ ህመም እጅግ የተጎዱ ከ35 በላይ ህመምተኞች በወቅቱ ለመመልከት ችለናል፡፡  እነዚህን  ወገኖች  ዘር ፤  ቀለም ፤  ሃይማኖትና ፤  ጾታ   ሳይለይ   ጌርጌሴኖን    የአዕምሮ  ህሙማን  መርጃ  ማኅበር  የተቻለውን ያህል  እያደረገ ይገኛል፡፡

እኛም ወገኖቻችንን ገንዘብ ያለን በገንዘባችን ፤ ጉልበት ያለን በጉልበታችን ፤ እውቀት ያለን በእውቀታችን በህመም ፤ በችግር እና በተለያየ ምክንያት በየቦታው ወድቀው የሚገኙ ሰዎችን በመመልከት የአቅምን ያህል በመርዳት ሰብአዊ እና ሃይማኖታዊ ሃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል፡፡

እግዚአብሔር አምላክ በማዕከሉ የሚገኙ ህሙማንን ፈጽሞ ከህመማቸው ይፈውሳቸው፡፡ እርስዎም በማዕከሉ በመገኝት የመልካም ስራቸው ተባባሪ ይሆኑ ዘንድ ‹‹አንድ አድርገን›› ጥሪዋን ታስተላልፋለች፡፡



አድራሻ ፡- አዲስ አበባ  ወደ እንጦጦ ማርያም / ሲሄዱ ቁስቋም 17 ቁጥር አውቶቡስ  ማዞሪያ
ለበለጠ መረጃ  

አቶ መለሰ አየለ + 251 912 18 88 76

+251 922 82 12 35  / 251 118 70 39 27

በገንዘብ አስተዋዕጾ ማድረግ  

ጌርጌሴኖን አዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር 
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር፦ 0170976663500
አዲስ አበባ 
E-mail:- gergesenon@gmail.com / meleseayele82@gmail.com



No comments:

Post a Comment