Friday, September 27, 2013

የእግዚአብሔርን ተዓምር ተመልከቱ



(አንድ አድርገን መስከረም 17 2006 ዓ.ም)፡- ቦታው ሶርያ ሀገር ነው፡፡ የቤተክርስቲያኑ ስም saydania ይባላል:: ቤተክርስቲያኒቱ እንደተለመደው የዘወትር ፀሎት ለህዝቡ ፤ ለዓለምም እያደረሰች ባለችበት ሰዓት አንድ ሰው ወደ አንድ መነኩሴ እማሆይ Marina Almaloof ቀርቦ ‹‹ስለት ለመስጠት ነበር እባክዎን ይሄን ብር ሳጥን ውስጥ ያስገቡልኝ›› ይላቸዋል  በእጅ የያዘውን 160. የሆነውን ሻማ ‹‹ይሄን ደግሞ በስዕለ ማርያም ፌት ያብሩልኝ እኔ በጣም ሰለምቸኩል ነው›› ይልና በፍጥነት ከቤተመቅደሱ ይወጣል ፡፡ መነኩሴዋም ክብሪት በማንሳት ‹‹አቤቱ የሰራዊት ጌታ የዚህን ሰው ስለቱን ተቀበለው›› እያሉ ክብሪቱን ጫሩ ፤ ሻማው ጫፍ አቀረቡት ሻማው ሳይቃጠል ክብሪቱ ተቃጥሎ አለቀ ፤ በድጋሚ ሞከሩ ሞከሩ ሻማው ባለመቃጠሉ እየተገረሙ ከወደ ቤተክርስቲያኒቱ ደጃፍ ጩህት ተሰማ መነኩሴዋም ወደ ጩህት ቦታው በፍጥነት ወጡ ፤ ከታች ከበስተመጨረሻ ደረጃው ላይ አንድ ሰው ወድቆ የሞተ ሰው ተመለከቱ፡፡‹‹ ይሄ አሁን ስለት የሰጠኝ ሰውየ አይደለምን?›› በማለት የተፈጠረውን ሁኔታ ለማስረዳት ስልክ ለአካባቢው ፖሊስ ደወሉ ፤ ፖሊስም በፍጥነት ቦታው ላይ በመገኝት ነገሩን አጣራ ፤ ሁኔታውን ሁሉ ከመነኩሴይቱ በመጠየቅ ተረዳ ፤ ልጁ ቤተመቅደስ ይዞ ገብቶ እንዲለኮስ የፈለገውን ሻማ ፖሊስ ተቀብሎ ሲመረምረው በውስጡ ዳይናሜት TNT የተባለ አደገኛ ተቀጣጣይ ፈንጆች የተሞላ ሁኖ አገኝው፡፡ ይህን ያደረገውን ሰው የሚያውቅ አልተገኝም ፤ ሰውየው በልብ ድካም ነው የሞተው ተባለ ፤ ወላዲተ አምላክ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ህዝቧንም ቤተክርስቲያኑንም በዚህ ተዓምር ታደገች ልመናዋ ምልጃዋ በእኛ ላይ  ይሁን አሜን! 

2 comments:

  1. ቃለ ሕይወት ያሰማልን ! እንደዚህ ዓይነት ታምር ከሰማን ቆይተን ነበር በርቱ ለእግዚአብሔር ምን ይሳነዋል ገና ብዙ እናያለን ከእናቱ ጋር ብዙ ታምራትን ያደርጋሉ !!!!!!

    ReplyDelete
  2. ድንግል የኛንም አገር ትታደገን

    ReplyDelete