Monday, June 16, 2014

‹‹የተቀደሰችው ደጅ ከዚህ በላይ መርከስን ማስተናገድ የለባትም›› መምህር ተስፋዬ ሸዋዬ

  • ኢትዮጵያ እና ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖት ተለያይተው አያውቁም፡፡
  • ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ኢትዮጵያ ከነበራት የቀድሞ ስፋትዋ ቢያንስ አሁን ባለችበት ቅርጽና ይዘት እንድትቆይ በማድረግ ባለውለታ ናት እንጂ ሀገር ያደኸየች አይደለችም፡፡
  • ድርሳንና ገድላትን የሚነቅፏቸው ከርዕይ ያልደረሱ ጣዕመ ጸጋ ያልቀመሱ ዐይኑ ግንባር ሆኖ እንደተፈጠረው የጤሜዎስ ልጅ በርጤሜዎስ ግንባር የሆነ ዐይነ ነፍሳቸው በክርስቶስ ጣት ያልተዳሰሰ በመለኮት ምራቅ ያልራሰ ሰዎች ናቸው፡፡
  • …. ከባለቤቱ የእግር ሰላም አንዲት ጠብታ እንዳይቀርባት በፍቃዷ ከግብጽ ጳጳሳትን ስታስመጣ ኖራለች፡፡ ያስገደዳት አልነበረም የአባቶቻቸውን ቃል ውሉድ በፍቅር ሲጠብቁት ኑረዋል እንጂ ከግብጻውያን ያገኝችው ትምህርት የለም፡፡


(አንድ አድርገን ሰኔ 9 2006 ዓ.ም)፡-
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከሃይማኖቷ ፤ አስተምህሮዋ እና ቀኖና ውጪ የሆኑ ድርጊቶች በመስፋፋት ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህን ድርጊት በሚመለከት መምህር ተስፋዬ ሸዋዬን እንደ አንድ የእምነቱ ተከታይ ግለሰብ ያላቸውን ሃይማኖታዊ አስተያየት ለፎከስ መጽሔት ሰጥተው ነበር፡፡ የዚህንም ቃለ መጠይቅ ምላሽ እንደሚመለከተው አቅርበነዋል፡፡

ፎከስ፡- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት መቼ እና እንዴት ተጀመረ?
መምህር ተስፋዬ፡- ኢትዮጵያ ሀገረ እግዚአብሔር የምትባልበት ምክንያት በሦስቱም ሕግጋት ታውቀው ስለነበረ ነው፡፡ እነዚሁ ሕገ ልቡና ፤ ሕገ ኦሪት እና ሕገ ወንጌል ናቸው፡፡ ሕገ ኦሪት ስትሰራ ኢትዮጵያዊቷ ከሙሴ ጋር ነበረች፡፡ ከእርሷ ወገን የምትቆጠር ንግሥት ሳባም ከሰሎሞን ጋር የነበረውን ጥበበ እግዚአብሔር ለማየት ወደ ኢየሩሳሌም እንደሄደች ከዚያም ልጇ ሕገ እግዚአብሔር በራሱ በእሳት ጣት የተጻፈበትን ጽላት በዘመኗ እንዳመጣ የሚያገለግሉ ካህናትም አብረው እንደመጡ ተደጋግሞ የነገለጸ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት በአጸደ ነፍስ ሳለች ባለቤቱ ያላቸውን ባልሰሙ ትውልድ ላይ የመፍረድ ስልጣን የሰጣት ናት፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የወልደ እግዚአብሔር ሰው  መሆን በኢትዮጵያ ሲጠበቅ ቆይቷል፡፡ አዳምንና ልጆቹን ከፍዳና ከመርገም ከዘላለም ኩነኔ ሊታደግ በሁለት ወገን ዘላለማዊት ድንግል ከሆነች ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ በመዋሕድ እንደኛው ሰው ሥጋም ሆኖ በተወለደ በሁለተኛው ዓመቱ ከአዳም በፊት የገነት በር ለተከፈተለት  በቀኙ ለተሰቀለው ሰው ቃል ኪዳን በመግባት በግብጽ በኩል ወደ ኢትዮጵያ በመጣ ጊዜ መልኩን ዐይታ በሕጻን አንደበቱ ያስተማራትን ትምህርት የሠራላትን ገቢረ ተዓምራት አስተውላና ተረድታ የባሕርይ አምላክነቱን አምና በክብር አስተናግዳዋለች፡፡ መንፈስ ቅዱስ በጽርሀ ፅዮን በወረደ ጊዜ ለመገኝቷ  አቡነ ዘበሰማያት በቋንቋዋ በግዕዝ ተጽፎ መገኝቱ ምስክር ነው፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ኢትዮጵያ እና ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖት ተለያይተው አያውቁም፡፡

Saturday, June 14, 2014

‹‹አንድ ሚሊዮን ወጣትም ቢሆን የፈለገበት ይድረስ ፤ ምንጣፍ አነጠፈም አላነጠፈም የፈለገበት ይድረስ›› የጠቅላይ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ


  •  " ገመድ የምትበላ ብትሄድ ጠፍር የምትበላ ትመጣለችሀገርኛ ብሂል

(ፋክት ቅዳሜ ግንቦት 7 2006 ዓ.ም)፡- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ወጣቶች ማኅበራት ሕብረት ፍቃድ መሰረዙ ተሰማ፡፡ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ግንቦት 8 ቀን 2006 ዓ.ም ለሕብረቱ በጻፈው ደብዳቤ ላይ እንደገለጸው ፤ ሕብረቱ ከሕገ-ቤተክርስቲያን እና ከቃለ አዋዲው ሕግጋት ፍቃድ መሰረዙን ገልጿል፡፡

አባ ማትያት ፡- ከሕለተ ሙሴ ወደ ሕለተ ወርቅ


ከታደሰ ወርቁ
ቅዳሜ ሰኔ 7 2006 ዓ.ም ፋክት መጽሄት የተወሰ
  • አቡኑ ጉዱ ካሳን የሆኑ እስኪመስለን ድረስ የለውጥ አባት ተደርገው ተወሰዱ ፤ በቤተ ክርስያኒቱ ምሁራን ልጆች ተሳትፎ እየፈራረስ የነበረውን ጽመታዊ ቡድንን ከያለበት እየፈለጉ በማሰባሰብ ነፍስ ዘሩበት፡፡ቅዱስነታቸው ፤ ራሳቸውን ለአላስፈላጊ ተጽህኖ ያጋለጡበት ፈቃደኝነትና ዝግጁነት ቄሳራዊው ወገን ብቻ ሳይሆን ጽምታዊውም ቡድን ያልጠበቀው ምርኮ ኾነለት፡፡
  • ፓትያርኩ ቤተ ክርስቲያናችን ለመንፈሳዊ ተቋምነቷ የሚመጥኑ ሰዎች ሊመደቡላት እንደሚገባ ቢናገሩም በቅዱስነታቸው የሚታየው አቋም የለሽነትና አቅመ ቢስነት ከፍቶ አደባባይ ወጥቶ አሸማቃቂ ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡
  • ቅዱስነታቸውን በክብረ-ክህነት ላይ አመንዝረው ፤ ከአባቶቻችን አዋራጆች ፤ ምሁራን ልጆቻቸውን በጠራራ ጸሀይ ለማስገደል ጭምር ከሚያሴሩ ፤ ቤተ ክርስቲያኒቱን በግላጭ ከሚዘርፉና ከሚመዘብሩ እንዲሁም ለመሰረተ እምነቷ  ፤ ለሥርዓቷ ፤ ለትውፊቷና  ታሪኳ ግድ ከማይላቸው አማሳኞችና ጽልመታዊ ኃይሎች ጋር የተሰለፉት ሕለተ ሙሴን ጠልተው ሕለተ ወርቅን በማፍቀር አባዜ ነው፡፡


(አንድ አድርገን ሰኔ 7 2006 ዓ.ም)፡-በአዲስ ፓትርያርክ ፤ ዋና ጸሐፊ እና ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ሥራውን የጀመረው ቤተ ክህነት ባሳለፍነው ወርሀ ግንቦት አንደኛ አመቱን ይዟል፡፡ ይህው የአንድ ዓመት የሥራ ዘመን ገና ከጅምሩ ስለ ቤተ ክርስቲያኒቱ ተቋማዊ ለውጥ ብዙ የተለፈለፈበት ቢኾንም መሠረታዊ ችግሮቿን መፍታት ይቅርና አንዲት ክንድ አንኳን ፈቅ አላደረገውም፡፡ ዓመቱ ፤ በመልካም አስተዳዳር እጦት መንስኤ የኾኑት ብልሹ አሰራር - ሙስና- ጎጠኝነት ከየትኛውም ጊዜ በላይ ጎልተው የታዩበት ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላለፉት ኻያ አንድ አመታት በርዕሰ አበውነት ‹ሲገዙ› የነበሩትን የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስን ሞትን አስከትሎ ስድስተኛውን ዘመነ ፕትርክና  የምደባ ያህል  የተረከቡት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ  የቤተ ክርስቲያኒቱን ቀናኢ ሊቃውንትና ምእመናን ለዘመናት ሲያንገሸግሽ የቆየውን አድሏዊ አሠራር ፤ ጎጠኝነትና ሙስና በመጠኑም ቢኾን ይፈታሉ የሚል ግምት ተሰጥቷቸው ነበር፡፡

Wednesday, June 4, 2014

መንግሥት በዋልድባ ገዳም በመሥራት ላይ ያለውን የሥኳር ፕሮጀክት 12 በመቶ ማጠናቀቁን ገለጸ


(አንድ አድርገን ግንቦት 28 2006 ዓ.ም)፡- ከወር በፊት መንግሥት በዋልድባ ገዳም በመሰራት ላይ ላለው የሥኳር ፕሮጀክር  ቻይና መንግሥት ሥራውን ማጠናቀቂያ የገንዘብ ብድር ማግኝቱ ይታወቃል፡፡ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ የኢቲቪ የምሽት ዜና ላይ የሥኳር ፕሮጀክቱ 12 ከመቶኛ መጠናቀቁን ተገልጿል፡፡ ከወር በፊት ቦታው ላይ በአካል ደርሰው ከመጡ ምዕመናኖች እንደተረዳነው ከሆነ በገዳሙ የሚገኙ መናንያን ጋር በመቅረብ መረጃ ማግኝት አስቸጋሪ ቢሆንም መነኮሳቱ የዘወትር የሥራ መርሃ ግብር በተጨማሪ  በጾምና በጸሎት መጠመዳቸውን ገዳሙ ድረስ ደርሰው ከመጡ ሰዎች ለመረዳት ችለናል፡፡ በቦታው ከሄዱ ሰዎች አንዱ አንድን አባት ስለ ሁኔታው ለመጠየቅ ሞክሮ ‹‹ጸልዩ›› ተብለናል ስለዚህ ‹‹ሁሉንም ነገር በሂደት የምናየው ነገር ይሆናል እኛ እየጸለይን ነው፡፡›› በማለት መልስ ሰጥተውታል፡፡

Tuesday, June 3, 2014

‹‹ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት››



 (አንድ አድርገን ግንቦት 26 2004 ዓ.ም)፡-
ፕሮፌሰር ታደሰ ይባላሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ፕሮፌሰር  ሲሆኑ የዩኒቨርሲቲው የመጻሕፍት ዝግጀት ተቋም ዳይሬክተርና ዋና አዘጋጅ በመሆን አገልግለዋል፡፡ በአሜሪካ ሀገር በኮኔል ፤ ኖርዝዌስት ዩኒቨርሲቲ ኢሊኖይ ስቴት ዩኒቨርሲቲ በጎብኝ ፕሮፌሰርነት ከማስተማር በተጨማሪ በሳባቲክና ፈቃዳቸውን  በፈረንሳይ ሀገር ባሳለፉት ዓመት በታዋቂው ኮሌዥ ዲፍራንስና በፓሪስ ዩኒቨርሲቲ እየተጋበዙ ጥናታዊ ጽሑፎችን ያደረጉ ምሁር ናቸው፡፡ እኚው ፕሮፌሰር በጦቢያ መጽሔት ቅጽ 5 ቁጥር 10 1990 ዓ.ም በአምስተኛው የፕትርክና ዘመን ለብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የተሰጠውን ‹‹ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት››ን ማዕረግ አሁንም የቀጠለው መጠሪያ በሚመለከት ተጠይቀው የመለሱት መልስ ለማስቃኝት ወደድን ፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ‹‹ሊቀ ጳጰስ ዘአክሱም›› የሚለው መጠሪያ ላይም ውዝግብ እንደነበር የምናስታውሰው ነገር ነው፡፡

Monday, June 2, 2014

የሲኖዶስ ጉባኤ በፓትርያርኩና ጳጳሳቱ ፍጥጫ ተቋጨ

Addis Admass
  • ጳጳሳት የፓትርያርኩን የማኅበረ ቅዱሳን ደንብ ማሻሻያ ቅድመ ኹኔታ አልተቀበሉትም
  • ‹‹ቅድመ ኹኔታው የማኅበሩን አገልግሎት የሚያቀጭጭና በሒደትም የሚያስቆም ነው›› /ታዛቢዎች/
የማኅበረ ቅዱሳን መተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ረቂቅን እንደ አንድ አጀንዳ የያዘው የዘንድሮው የሲኖዶሱ የርክበ ካህናት ጉባኤ ከረቂቁ ጋር በተያያዘ በፓትርያርኩና በሊቃነ ጳጳሳቱ መካከል በተፈጠረ ፍጥጫ መጠናቀቁ ተገለጸ፡፡ 

የጎመጀው ፤ የደነዘዘው እና የደነቆረው ሕዝብ……

ኃይለጊዮርጊስ ማሞ
(የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት ትምህርት ክፍል መምህር)

(አንድ አድርገን ግንቦት 25 2006 ዓ.ም)፡- ሰሞኑን የከተማችን ወሬ ሆኖ የከረመው አንድ አስገራሚ(እንደዚህ ጸሐፊ እምነት አሳፋሪ) ክስተት ነበር፡፡ ክስተቱ አንድ ዜግነቱ የማላዊ የሆነ “ነብይ” ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣቱ ጋር በተያያዘ በሚሊኒየምና እንዲሁም በነጋታው ‹‹መድህን ዲኮር›› በተባለ አዳራሽ የታየ “ሕዝባዊ ውርደት” ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ እንደዚህ አይነት ክስተቶችን ልብ ብሎ ለተመለከተ ሃገሪቱ ጠባቂ የሌላትና ማንም እንደፈለገ እየገባና እየወጣ የሚፈነጭባት ‹‹መሰማሪያ›› ትመስለዋች፡፡ በተለይም ደግሞ የሕዝብ ድህነት ፤ መጎምዥት ፤ መንፋሰዊ ክስረትና ውድቀትን ተገን አድርጎ በየስፍራው የሚነሳው “ሃገር በቀል ቦጥቧጭ” አልበቃ ብሎ ‹‹አለም አቀፉን›› ደግሞ እየጋበዙ  በማምጣት እንዲህ ሕዝብን መጫወቻ ማድረግን ስንሰማ ከዚህ በላይ ሕዝብ የራሱን ክብር ከጭቃ የሚጥልበት ትንሽነት ከወዴት ሊመጣ ይችላል? በማለት ለመጠየቅ እንገደዳለን፡፡

በአንድ ወቅት ‹‹ፓስተርና ፖስተር›› ሲባልበት የነበረው ከተማ ዛሬ “ወደ ነቢያት ጉባኤ” ተቀይሮ ሁሉ በየፊናው  የነብይነት ካባን በየአደባባዩ እየተጎናጸፈ የሕዝቡን መጎምዥትና  ጭንቀት ተገን አድርጎ መቆምን አስተማማኝ የትርፍ መስክ ሲያደርገው “ኧረ ሃይ ባይ የለም ወይ?” የሚያስብል ሆኗል፡፡ እርግጥ ነው ትውልድና ዘመን ብዙ ዓይት መልክ ያለው ክስረት  ውስጥ ለመግባቱ በድፍረት ብቻ ሳይሆን በተሰበረ ልብ እንናገራለን፡፡ ዛሬ የመንፈሳዊነት አገልግሎት በኢትዮጵያ ከሰማዩ ይልቅ የምድራዊውን ሕይወት ጥያቄ ምላሽ በመስጠት የተያዘ የትርፍ መስክ ያደረገውም ይኽው ክስረታችን ነው፡፡ ደርግ የሃይማኖት ነጻነትን ነፍጎ ሕዝቡን ኮሚኒስት (ኢ-አማኒ) ለማድረግ ሲታትር በዚያ ዘመመንና ትውልድ በመንፈሳዊነት ጸንተው ዋጋ የከፈሉ በርካቶች ነበሩ፡፡ ኢህአዴግ ደግሞ መጣና “የሃይማኖት ነጻነት”  በማለት ሲያውጅ “ዋጋ የተከፈለበት” መንፈሳዊነት “ዋጋ የሚያስከፍሉበት” ሆኖ ቀረ፡፡ በመሆኑም ለዚህ አይነቱ በሀገር ላይ ለመጣ መንፈሣዊ ብቻ ሳይሆን  የማንነት ውድቀት ተጠያቂው ማነው? ወዴትስ እየሄድን ይሆን ?

Friday, May 30, 2014

የቤተ ክህነቱ ጨለምተኛ ምሁራዊ ድባብ ፡ Cynical Intellectual Atmosphere

                                                              
                                                              በታደሰ ወርቁ ተጻፈ
  • ዛሬ ሊቃውንቱ የቤተክርስቲያኗ መቁሰል አልታይ ብሏችዋልና ቤተክርስቲያን አለቃ አያሌውን ከሙታን መንደር ትጣራለች፡፡

(አንድ አድርገን ግንቦት 23 2006 ዓ.ም)፡- በዚህ ዐውድ(Context)ምሁር የምለው ከቤተ ክርስቲያኒቱ የአብነት ትምህርት ቤቶች ሊቅነታቸውን ያስመሰከሩ ፤ ከመንፈሳዊ ኮሌጆች የተመረቁ እንዲሁም በቤተ ክርስቲያኒቱ ዙሪያ ጥናትና ምርምር አድርገው የጥናት ወረቀቶቻቸውን ያበረከቱ ፤ መጻሕፍትን ያሳተሙትን ጭምር ነው፡፡ በጥቅሉ በቤተ ክርስቲያኒቱ በአዕምሮ ሥራ ላይ የተሰማሩትን ነው፡፡

በዚህ መልኩ ያስቀመጥናቸው ሊቃውንት ቁጥር በአንጻራዊነት እያደገ ቢሄድም በቤተ ክርስቲያኒቱ እና በምእመኑ ውስጥ ቀድሞ የነበራቸው ቦታና የኑሮ ደረጃ በማሽቆልቆል ላይ ይገኛል፡፡ አንዳንዶቹም ሊቃውንት በቤተ ክርስቲያኒቱ  አገልግሎታቸውን እየሰጡ ቢሆኑም  በአሁን ጊዜ በቤተ ክርስቲኒቱ ውስጥ እንደሚታየው የቀድሞውን የመንፈስ ልዕልና እና ሐሳባዊ መሪነት አጥተዋል፡፡ ለመኖር የሚያስፈልጋቸውን ከማድረግ በተረፈ ምሁር የሚያሰኛቸውን ተግባር የሚፈጽ አሉ ብሎ ለመናገር አያስደፍርም፡፡

Thursday, May 29, 2014

የቅዱስ ሲኖዶስ “ሰብኣዊ ገጽ”


በታደሰ ወርቁ ተጻፈ
(አንድ አድርገን ግንቦት 21 2006 ዓ.ም)፡- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኦሪት የታዘዘውን ፤ በወንጌል የተፈጸመውን መሠረታዊና አማናዊ ሕግ በተገቢው መልኩ ስትፈጽም ቆይታለች፡፡ በዚህ አግባብም ካህናቷንና ምዕመኗን  ለዘመናት ስታስተዳድር ቆይታለች፡፡ዐይነተኛ አገልግሎቷም እስከ ዘመናችን ድረስ ጉልህ ሆኖ ይታያል፡፡

ቤተ ክርስቲያኒቱ በየጊዜው የደረሰባት መስክ ወለድ ትግልና ድካም አሸንፋ ፤ መንፈሳዊ አገልግሎቷ እስከ ጽንፍ ኢትዮጵያ እና ዓለም ዳርቻ ሲሰማና ሲነገር ፤ ሲመለክና ሲከበር የኖረው ሰብኣዊ ገጻቸውን በሃይማኖት ገጽ ልዕልና ባሸነፉ አባቶቿ ነጻ ፤ ጠንካራ እና ቆራጥ አመራር ነው፡፡የቤተ ክርስቲያኒቱ ዐይናማ ሊቃውንት ሰብኣዊ ገጻቸውን በመንፈስና በሞራል ልዕልና ገርተው ለአንድ ሺህ ስድስት መቶ ዓመታት ቤተ ክርስቲያቱን ተጭኗት የነበረውን የግብጻውያንን ቀንበር በማወገድ “ለአንዲት ነጻ አገር አንድ ፓርላማ እንዳላት ሁሉ ለአንዲት ነጻ ቤተ ክርስቲያን አንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ብቻ” በሚል የራሷ ቅዱስ ሲኖዶስ እንዲኖራት አስችለዋታል፡፡

‹‹ቤተ ጊዮርጊስ›› ከዓለም 19 አስደናቂ ቦታዎች አንዱ ሆነ



(ሪፖርተር ግንቦት 20 2006 ዓ.ም)፡-  በቅዱስ ላሊበላ ከተማ የሚገኘው ቤተ ጊዮርጊስ ውቅር ቤተ ክርስቲያን በዓለም ላይ ካሉ እጅግ አስደናቂ የተቀደሱ ሥፍራዎች ውስጥ ተካተተ፡፡

በቅርቡ ሀፊንግተን ፖስት ባወጣው መረጃ መሠረት፣ በዓለም ላይ ካሉና የተመልካችን ቀልብ ገዝተው ከተገኙ 19 ቦታዎች ውስጥ ቤተ ጊዮርጊስ አንዱ ሆኗል፡፡ 12ኛው መቶ ክፍለ ዘመን (800 ዓመታት በፊት) በአፄ ላሊበላ ከተሠሩት 12 ውቅር አብያተ ክርስቲያናት አንዱ የሆነው ቤተ ጊዮርጊስ፣ ከሌሎቹ በተለየ በተደጋጋሚ በጎብኚዎች ፎቶግራፍ የተነሳ ሲሆን፣ የበርካታ ቱሪስቶች መዳረሻ በመሆን ከተቀሩት አብያተ ክርስቲያኖች የበለጠ ዝናን የተቀዳጀ ነው፡፡