Tuesday, October 18, 2022

"ተናበን እንዳንሰራ እንቅፋት የሆነብን ምንድን ነው?" ሲሉ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ ጠየቁ ።

 

ጥቅምት 7 ቀን 2015 . (አዲስ አበባ) :- የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም በባለፈው በጀት ዓመት የተሰሩ በርካታ ክንዋኔዎችን ዛሬ ጥቅምት 7 ቀን 2015 . 41ኛው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በጠቅላይ ቤተ ክህነት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ በተካሄደበት ላይ በሪፖርት አቅርበዋል ። ብፁዕነታቸው በሪፖርቱ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ሐዋርያዊ ክንውን ሐዋርያዊ ተልዕኮና መንፈሳዊ አገልግሎትን በተመለከተ የተሰሩ ሥራዎችን ፣በአስተዳደርና ፋይናንስ ዘርፍ የተሰሩ ስራዎችን ፣የምግባረ ሠናይ ዘርፍን በተመለከተ የልማት ድርጅቶችን እነዚህንና ሌሎችም መሰል ተግባራትን በተመለከተ በንባብ አሰምተዋል

ብፁዕነታቸው በመጨረሻም መሠረታዊ የመወያያ አጀንዳዎች የሚሆኑ መነሻ ሐሳቦችን አቅርበዋል። ብፁዕነታቸው ካቀረቧቸው መነሻ ሀሳቦች መካከልም


Ø  ስለ ሀገራችን ሰላም የቤተ ክርስቲያን አስተዋጽኦ ምን ይሁን ?

Ø  በቤተክርስቲያን እና በምእመናን የሚደርሰውን ግፍ በምን መልኩ ማስቆም ይቻላል ?

Ø  የቤተ ክርስቲያን ሕልውና ለማረጋገጥ (አብነት ትምህርት ቤት ለማስቀጥል፤ ሰንበት ትምህርትን ከማጠናከር አንጻር፤ ስብከተ ወንጌል ከማስፋፋት አንጻር ?)

Ø  በጀት አጠቃቀም ላይ ያለውን ችግር እንዴት እንፍታው?

Ø  የቤተ ክርስቲያንን ምጣኔ ሀብት እንዴት እንጠብቀው?

Ø  ከመንበረ ፖትርያርክ እስከ አጥቢያ ድረስ ተናበን እንዳንሰራ እንቅፋት የሆነብን ምንድን ነው ?ተናቦስ ለመሥራት ምን እናድርግ ?

Ø  የቤተ ክርስቲያንን ክብር እንዴት ጠብቀን እናስጠብቅ ?

Ø  ቤተ ክርስቲያናችን ለተጎዱት ከመድረስ ይልቅ ጉዳት ደረሰብኝ ባይ ሆናለች ስለዚህ ከዚህ ለመላቀቅ መፍትሄው ምንድን ነው ?

Ø  ሙስናን እንዴት አድርገን ከቤተ ክርስቲያን እናላቀው? የሚሉ መሰል ጥያቄዎች ከብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ሪፓርት ቀጥሎ ለተሰብሳቢዎቹ የተሰጠ ሲሆን ከቀትር በኋላ ውይይት ይድረግባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

 

No comments:

Post a Comment