Friday, March 6, 2015

መንግሥት ‹‹የእሬቻ በዓል እና የሐውልት ተከላ ሥነ ሥርዐት በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የጠበል ስፍራ ይከናወናል ተብሎ በመንግሥት ብዙኃን መገናኛ መተላለፉን አላውቅም›› አለ

  • ‹‹በመንግሥት ብዙኃን ስለመተላለፉ ማረጋገጥ ከፈለጋችው ሲተላለፍ የተቀረጽው በእጃችን ስላላ ልንሰጣችሁ እንችላለን ፤›› የገዳሙ አስተዳደር ጽ/ቤት
  •   ‹‹ በሥልጣን ያላግባብ ሃይማኖታቸውን መጥቀም የሚፈልጉ አንዳንድ የክልሉ ባለሥልጣናት ያደረጉት ሊሆን ይችላል እንጂ መንግሥት በፍጹም ሊያደርገው እንደማይችል ልናረጋግጥላችው እንወዳለን ፤›› የመንግሥት ባለሥልጣናቱ
መንግሥት ‹‹የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የባሕልና ቱሪዝም ቢሮ ከክልሉ የገዳ ሥርዐት ጽ/ቤት ጋራ በመቀናጀት የእሬቻ በዓልና የሐውልት ተከላ ሥነ ሥርዐት መጋቢት 30 ቀን 2007 ዓ.ም በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የጠበል ስፍራ አከናውናለ ›› ብሎ መስከረም 15 ቀን 2007 ዓ.ም በመንግሥት ብዙኃን የሰጠውን መግለጫ እንደማያውቀው አስታወቀ ፡፡

Thursday, March 5, 2015

ስለ ‹‹ዝቋላ ደብረ ከዋክብት›› ቤተ ክርስቲያን ትጣራለች ‹5›





      ለደብረ ከዋክብት የመፍትሔ ሀሳቦች ‹4›


      ደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ከተገደመ ፰፻፸፯ ዓመታት እንዳስቆጠረ የገዳሙ ታሪክ ያስረዳል፡፡ በበርካታ የኢትዮጵያ ግዛቶች እንደሚገኙት ገዳማት እና አድባራት በሀገሪቱ ከሚገኙ ከፍተኛ ተራሮች አንዱ በሆነው በዝቋላ ተራራ ላይ ከመመሥረቱ ባሻገር ከላይ ከአናቱ በፈዋሴ ድውያን የጠበል ሐይቅ ዙሪያውን ከእግረ ተራራው ጀምሮ እስከ አናቱ ድረስ እንደ መሥራቹ እንደ አቡነ ገብረመንፈስቅዱስ የጸጋ ልብስ በተንዘረፈፈ አጸደ ሐምል የተሸለመ ዐቢይ ቅዱስ ገዳም ነው፡፡

      የክተት ጥሪ ወደ ዝቋላ ገዳም ‹3›

      የካቲት 26 2007


      በዝቋላ ገዳም የተነሳው ሰደድ እሳት አሁንም ድረስ ያልጠፋ ስለሆነ እሳቱን ለማጥፋት እና ኦርቶዶክሳዊ ግዴታችንን ለመወጣት እኛ ኦርቶዶክሳዊያን እና ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በነገው ዕለት ማለትም 27/06/07 . ከጠዋቱ አንድ ሰዓት በመስቀል አደባባይ ተገናኝተን ለመሄድ ተዘጋጅተናል ስለሆነም ወደ ቦታው ለመሄድ የምትሹ በቦታው እና በሰዓቱ እንድንገናኝ ይሁን!!!

                *የመጓጓዣ መኪና በነፃ ተዘጋጅቶ ይጠብቀናል*

       የቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ መገጣጠሚያ ድርጅት ቀደም ሲል በገባው ቃል መሠረት አሁን ከደብረዘይት ከተማ ሁለት ቦቴዎችን በማንቀሳቀስ ወደስፍራው እንዲያመሩ እያደረገ ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓት አንደኛው ቦቴ ሺህ ሊትር ውኃ ጭኖ ድሬ እየተባለ የሚጠራውን አካባቢ አልፎ ወደ ዝቋላ እያቆራረጠ ሲሆን ሁለተኛው ቦቴ ደግሞ ውኃ እየሞላ መኾኑ ታውቋል፡፡ ከመሣሪያው በተጨማሪ የበኩሉን የሰው ኃይል ድጋፍ እንደአስፈላጊነቱ ለማድረግም ቃል መግባቱን ሰምተናል፡፡ ይኽንን የፈቀዱት ኃላፊዎች እንዳስረዱት ከኾነ ይኽ ሀገራዊ ጉዳይ በመኾኑ እና የዜግነት ግዴታም ነው፡፡ ጉዳያችን ስለኾነ ወስነናል ብለዋል፡፡

      ስለ ዝቋላ ደብረ ከዋክብት ‹2›


       ከዲ/ን አባይነህ ካሴ
      ንዑ ተጋባእክሙ
      በደብረ ከዋክብት ሀገርክሙ
      ክተት! ወደ ደብረከዋክብት

      ጀግናን ቀን ይወልደዋል፡፡ ቀን ማለት ጭንቅ ሰዓት፡፡ ሁኔታዎችን ተቋቁሞ ገድል የሚፈጽም፡፡ አሁን ብዙ ጀግኖች ደብረ ከዋክብት ገብተዋል፡፡ ክንዳቸው እስኪዝል ከእሰቱ ጋር ግብግብ ገትመ አድረዋል፡፡ ተተኪ ደጀን ግን የግድ ያስፈልጋቸዋል፡፡ እንድረስላቸው እና እኛም ከበረከቱ እንሳተፍ፡፡

      እንደዚህ ዓይነት አጋጣሚዎች የሚገኙት ከእልፍ አንድ ቀን ነው፡፡ እንዳያመልጡን እና እንዳያስቆጩን ያስፈልጋል፡፡ በቅርብ ያላችሁ እቦታው ድረስ በመግባት አግዙ፡፡ ከየሥራ ገበታችሁ አስፈቅዳችሁ ግቡ፡፡ ቤተ ክርስቲያን እዚያው ትፈልጋችኋለች፡፡ ባለመኪኖች በተለይ ፍጥነት የተመላበት ርምጃ ትወስዱ ዘንድ እንጠይቃለን፡፡

      ስለ ዝቋላ ደብረ ከዋክብት ‹1›


       
      ከዲ/ን አባይነህ ካሴ
      አስቸጋሪው እሳት ጋብ አለ እንጂ አሁንም አልጠፋም፡፡ ለጊዜው እዚያው ገደሉ ውስጥ ተገትቶ ይገኛል፡፡ እሳቱ ያለበት ቦታ ላይ ለመድረስ ባለመቻሉ ሌሊቱን ሙሉ የዙሪያ ገብ ምንጠራ ሲካሄድ አድሯል፡፡ የገደሉ አካባቢ እያልን የምንጠራው ስፍራ በቀላሉ የሚገመት ሳይኾን ወደ ሃያ ሺህ ሄክታር የሚጠጋ ቦታ ይሸፍናል፡፡ ቁጥራቸው ፭፻ በላይ የኾኑ ሰዎች እሳቱን ለማጥፋት ወደ ዝቋላ ገዳም ገብተው አድረዋል፡፡ የቦታው ገደላማነት፣ ጨለማውና ጫካው ተደማምሮ እስከመጠፋፋት ተደርሶ ነበር፡፡ከምሽቱ እስከ ሰዓት ድረስ ጨለማው ሳይበግራቸው በእግር በመኪና ወደ ገዳሙ የገቡ መኾናቸው ታውቋል፡፡

      Wednesday, March 4, 2015

      የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የባሕል እና ቱሪዝም ቢሮ በዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የጠበል ስፍራ‹‹ መጋቢት 30 ቀን 2007 ዓ.ም የበዓለ እሬቻን እና የሐውልት ተከላ ሥነ ሥርዐት አከናውናለሁ›› ማለቱ ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሣ፡፡



      ‹‹ … ሁለተኛው ዙር የእሬቻ በዓል ሥነ ሥርዐት በዝቋላ ተራራ እና በአከባቢው ይከበራል ፡፡›› – የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የባሕል እና ቱሪዝም ቢሮ

      ‹‹ … የእሬቻ በዓል በዝቋላ ገዳም እንደሚካሄድ በመንግሥት ብዙኃን መገናኛ የገዳ ሥርዐት /ቤት ማስተላለፍ ተገቢ አይደለም፡፡›› ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

      ‹‹ …ችግሩ ከመፈጠሩ በፊት በተገለጸበት የመንግሥት ብዙኃን መገናኛ ማረሚያ እንዲተላለፍ መደረግ አለበት ፡፡ ›› ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

      ‹‹ … ከጥንት ጀምሮ የዝቋላ ተራራ እና የጠበል ሐይቁ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ይዞታነት የታወቀ ነው ፡፡ ይህን እውነታ ወደ ጎን በመተውና የገዳሙን ሕጋዊ ባለቤትነት በመናቅ በማን አለብኝነት መንፈስ የተላለፈው ውሳኔ እኛንበእጅጉ አሳዝኖናል ፤ከፍተኛ የሆነ ሥጋትንም አጭሮብናል ፡፡ ›› ማኅበረ መነኮሳት

      ‹‹ … የእሬቻ በዓል በታሪካዊው ገዳም ላይ እንደሚካሄድ በመንግሥት ብዙኃን መገናኛ በመተላለፉ በገዳማውያኑና በሁሉም የቤተ ክርስቲያናችን ተከታዩች ዘንድ ቅሬታን አስከትሏል ፡፡ ›› ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ

      ‹‹ … ይኽን ችግር በተደጋጋሚ ጊዜ ለቀድሞው ፓትርያርክ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ እና ለመንግሥት አካላት ያመለክትን ቢሆንም ለችግሩ መሠረታዊ መፍትሔ እስከ አሁን ባለመሰጠቱ ለእንደዚህ ዐይነት ችግር ሊዳርገን ችሏል፡፡››ማኅበረ መነኮሳት

      ‹‹ … የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የባሕልና ቱሪዝም ቢሮ ግንቦት 23 ቀን 2004 .ምየገዳሙን አስተዳደር ደብረ ዘይት ድረስ ስብሰባ በመጥራት አስፈራርቷል ፡፡ ›› ማኅበረ መነኮሳት
      ‹‹ … ነገ ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ እንዳያመራ ከአሁኑ ጥንቃቄ ሊደረግበት የሚገባ ጉዳይ እንደሆነ እናምናለን ፡፡ ›› ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ

      ‹‹ … እናንት እኛ ቦታ ድረስ መጣችሁ እንጂ እኛ እናንተ ጋር አልመጣንም ፤ሀገራችንን ለቃችሁ ውጡ ፤ገዳሙ የነፍጠኛ ሃይማኖት እንጂ ለኦሮሞው ምኑ ነው ? ቦታው የእኛው እስከሆነ ድረስ አይደለም ሐውልት ማቆም ውሻ እንሰዋበታለን ፡፡ ››የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የባሕል እና ቱሪዝም ቢሮ

      ‹‹ … የዞኑ መስተዳደር ተወካዩች እና የጸጥታ ቢሮ ሓላፊዎቸ በተገኙበት የክልሉ ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ እና የገዳ ሥርዐት /ቤት ሓላፊዎች ኢትዮጵያዊነታችንን እና ወንድማማችነታችንን በሚገድልና ጫና ባለበት ሁኔታ በገዳሙ ጠበል እና ታቦት ማክበሪያ ስፍራ ሐውልት እንደሚያቆሙ በዛቻ አሳውቀውናል ፡፡ ›› ማኅበረ መነኮሳት
      ‹‹ …ታላቁ ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ደኅንነት ሲሉ ለብዙ ዓመታት የተጋደሉበት ቦታ ስማቸውና ታሪካቸው ተሸሮ ሌላ ሐውልት ሲተከል በዝምታ ለማየት አቅሙ የለንም ፡፡ገዳማችን ታፍሮና ተከብሮ ለእኛም ለማኅበረ መነኮሳቱም አስተማማኝ የሆነ ሕጋዊ ከለላና ጥበቃ እንዲደረግልን እንጠይቃለን ፡፡ ››ማኅበረ መነኮሳት