Sunday, September 7, 2014

ቸል የተባለው ውቅር


ወደ አማራ ክልል ሲጓዙ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን ጨምሮ በርካታ ሃይማኖታዊ ቦታዎች ይገኛሉ፡፡ በክልሉ በሚገኘው የዋግኽምራ ዞን ውስጥ ካሉ ጥንታዊ ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት ዘናቆ አቦ ገዳም፣ ዋሻ መድኃኔዓለም፣ ብርብር ጊዮርጊስ፣ ደብረ ፀሐይ ወይብላ ማርያም፣ ደብረ ሎዛ ውቅር ማርያምና አባ ዮሐንስ ይጠቀሳሉ፡፡ በዋግኽምራ ዞን በሚገኘው የሰቆጣ ከተማ ደግሞ ባር ኪዳነ ምሕረት ገዳምና ሌሎችም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ 
ውቅር መስቀለ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ኢትዮጵያን 495 እስከ 525 .. አስተዳድሮ በነበረው አፄ ካሌብ ዘመነ መንግሥት ከአንድ ቋጥኝ ድንጋይ ተፈልፍሎ የተሠራ ቤተ ክርስቲያን መሆኑ ይነገራል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ከላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት 500 ዓመት ቀድሞ እንደተሠራና የላሊበላ ፍልፍል ሕንፃዎች መነሻ ሊሆን እንደሚችል በቤተ ክርስቲያኑ ያሉ ሊቃውንት ያምናሉ፡፡
ቤተ ክርስቲያኑ በሰቆጣ ከተማ ደቡብ ምሥራቅ አቅጣጫ ያሉ ሰንሰለታማ ኮረብታዎች ያዋስነዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ሰባት ክፍሎች (ቅኔ ማህሌት፣ ቅድስትና መቅደሱን ጨምሮ) እና ጥንታዊ ሥዕሎች ያሉዋቸው አምስት ዐምዶች አሉ፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ የሚያስገቡ አራት በሮችና ዙሪያውን አሥራ አራት መስኮቶች ይገኛሉ፡፡
ቤተ ክርስቲያኑን ልዩ ከሚያደርጉት በዋነኛነት የሚጠቀሰው በውስጡ ያለው ዋሻ ነው፡፡ በጎበኘንበት ወቅት ዋሻው በእንጨት ርብራብ ተከድኖ ነበር፡፡ ዋሻው በሁለት አቅጣጫ (ሰሜንና ደቡብ) የተቦረቦረ ሲሆን፣ ቤተ ክርስቲያኑን ያስጎበኙን የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ሰላም መርሐጥበብ በየነ እንደሚሉት፣ አንደኛው በር ወደ ላሊበላ ሌላኛው ደግሞ ወደ አክሱም ይወስዳሉ፡፡

Wednesday, September 3, 2014

የግብረሰዶማዊነት አደጋ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ / ልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ሊቀ ጳጳስ

የግብረሰዶማዊነት አደጋ  እንዴት ይገለጻል?
ይህን ጥያቄ ከመመለሳችን በፊት ለግብረሰዶማዊነት የሚያበቁ ምክንያቶችንና የሚያስከትሉትን አስከፊ ጉዳቶች እናያለን። ምክንያቶቹን ስንጠይቅ የዕጾችና ሱሶች ተገዢ መሆን፣ ተገድዶ መደፈር፣ መጠለፍ፣ ተቃራኒ ጾታዎችን መጥላት፣ ለተመሳሳይ ጾታ መማረክ ወዘተ.. ሲሆን የሚያስከትላቸው አደጋዎችም ድብርት፣ ጭንቀት፣ ራስን መውቀስ፣ የህሊና ጸጸት፣ በከባድ በሽታ መለከፍ፣ ፊስቱላ፣ ራስን ማጥፋት፣ የኢኮኖሚ ውድቀት ወዘተናቸው።

Sunday, August 24, 2014

‹‹በያዛችሁትን ስልጣን ቤተክርስትያንን ከውድቀት ልታነሱበት ይገባችኋል ፤ ይህ ሳይሆን ከድጡ ወደ ማጡ የምትወስዷት ከሆነ ከታሪክ ተወቃሽነት አትተርፉም›› አለቃ አያሌው ታምሩ


አንድ አድርገን ነሐሴ 17 ፤ 2004 ዓ.ም 
፡- 
ቀኑ ህዳር 6 1985 ዓ.ም ነበር ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ሰሜን አቅጣጫ በምትገኝው በመንበረ መንግስት ቁስቋም ቤተክርስትያን ብዙ ህዝበ ክርስትያን ተሰብስቧል ፡፡ ምክንያቱ በዓለ ቁስቋምንና የጾመ ጽጌን ፍቺ በዓል ለማክበር ነበረ ፡፡ የዕለቱም አስተማሪ አለቃ አያሌው ታምሩ ነበሩ፡፡ አለቃ ‹‹በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን›› ብለው ጀመሩ፡፡ በትምህርታቸውም ስለ እመቤታችን ስደት ፤ ስለ ቁስቋም ታሪክ ፤ ወደ እየሩሳሌም ስለ መመለሷ ፤ ከእመቤታችን 300 ዓመት በኋላ በግብጽ ስለተሰራው የመታሰቢያ ቤተክርስትያን ፤ በዚህ በዓል ምክንያት ኢትዮጵያውያን ነገስታትና ንግስታት ስላደረጓቸው መንፈሳዊ ተሳትፎዎች ፤ ስመ ጥሩዋ ኢትዮጵያዊት ንግስት እቴጌ ምትዋብ በጎንደር ስላሰሯት የደብረ ቁስቋም ቤተክርስትያን  ፤ ስለ ጾመ ጽጌ ፤ ስለ ማህሌተ ጽጌ በዝርዝር አስተማሩ፡፡ ከዚያም በመቀጠል ፤ በእመቤታችን በቅድስት ማርያምና በልጇ ስደት በረከትን ካገኙ የኢትዮጵያ አውራጃዎች አንዱ የሆነው ምድረ ትግራይ ከሌሎች ቅዱሳን የኢትዮጵያ መካናት ጋር የተጣመረ የታሪክ ተዛምዶ ያለው ከመሆኑ ባሻገር ከታቦተ ጽዮን ጀምሮ ለኢትዮጵያ ለተሰጡ ልዩ ልዩ ስጋዊ እና መንፈሳዊ በረከቶች ምንጭና ቦይ ሆኖ የኖረ ነው ፡፡ ዋልድባ ገዳምም ይህን መንፈሳዊ በረከት ከሚገኝባቸው ቦታዎች አንዱ ነው ፤  በአሁኑ ወቅት ህዝቡ የተሰጠውን  ስጋዊ ስልጣን አገሪቱንና ቤተክርስትያንን ከውድቀት ለማንሳት ሊሰራበት ይገባል፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ህዝብና እግዚአብሔርን የሚያሳዝን ስራ ቢሰራ ግን ትዝብትና የታሪክ ተወቃሽነትን ያተርፋል ፤ ያለው ሰፊት ትምህርት ሰጥተዋል ፡፡(የአለቃ አያሌው ታምሩ የመንፈቅ መታሰቢያ ገጽ 26)

Thursday, August 21, 2014

‹‹ከዚህ በኋላ ያሉት ዘመናት ሰው ትንሳኤ ልቡና የሚነሳባቸው ማንም ሳያስተምረው ከመንፈስ ቅዱስ የተማረና ፈጣሪውን ያወቀ የሚሆንባቸው ናቸው፡፡›› መምህር ተስፋዬ ሸዋዬ


(አንድ አድርገን ነሐሴ 16 2006 ዓ.ም)
በኦሪት ዘፍጥረት እንደተጻፈው በድርሳነ ጽዮንም እንደተተረጎመው ብርሃን ከመፈጠሩና ማታና ጠዋት ፤ ቀንና ሌሊት ከመለየቱ አስቀድሞ ሰማይና ምድር ሳይለያዩ በአንድ ሁነው በጨለማ ይኖሩ እንደነበር ምድርም በውኃ ተሸፍና በላይዋ ላይ የእግዚአብሔር መንፈሰ ይሰፍን እንደነበር ተብራርቷል፡፡ ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር ብርሃን ይሁን ባለ ጊዜ ማታና ጠዋት ፤ ቀንና ሌሊት ሆነ ሰማይና ምድርም እንዲለያዩ በባለቤቱ ቃል ታዘዙ ተለያዩም፡፡ ከመላእክት በዓለሙ ካለውም ሥነፍጥረት በኋላ የሥነ ፍጥረት ፍጻሜ አዳምና ሔዋን ተፈጠሩ፡፡ ግዙፍ ሥጋና ረቂቅ ነፍስ ያላቸውም እንዲሆኑ እግዚአብሔር የሕይወትን መንፈስ እፍ አለባቸው፡፡ ልብ ንባብ እስትንፋስ ያላት ነፍስ ተሰጠቻቸው፡፡ በዚህም በተፈጠረው ፍጥረት ሁሉ ገዥነት ተሰጣቸው፡፡

Saturday, August 2, 2014

''ትናንትን ያሻገረን እግዚአብሔር ዛሬንም ያሳልፈናል''

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለሀገራችን ስልጣኔ በር ከፋች ሆና የኖረች ከመሆንዋም በላይ ዛሬ ላለው የዘመናዊ ስልጣኔም መሠረት የጣለች ባለውለታ ናት፡፡ ቀደምት የቤተ ክርስቲያን አበው ደከመን ሰለቸን ሳይሉ ዕረፍ ዘመን እስከገታቸው ድረስ ሲያገለግሉ ኖረው ቤተ ክርስቲያኒቱ አሁን ከምትገኝበት የዕድገት ደረጃ አድርሰዋታል፡፡
በዚህ ዘመንም የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች ሁሉ ይህን አስበው የተማሩትን ሃይማኖትና ሥርዓት ጠብቀውና አስጠብቀው ለሚመጣው ትውልድ ለማቆየት ኃላፊነት ያለባቸው መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ በእርግጥ ይህንን ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የማስጠበቅ ሂደት በውስጥም ሆነ በውጭ ሆነው ለማደናቀፍ ሌት ተቀን የሚዳክሩ ጠላቶች መኖራቸው እሙን ነው፡፡

Monday, July 28, 2014

‹‹መቅረዝ ዘተዋሕዶ - የውዳሴ ማርያም ማብራርያ›› መጽሐፍ በቅርብ ቀን በገበያ ላይ





መቅረዝ ዘተዋሕዶ መንፈሳዊት ድረ ገጽ አድራሻ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እምነት ፣ ሥርዓት ፤ ትውፊትና ታሪክ መሠረት ያደረጉ ትምህርታዊ የሆኑ ጽሑፎች የዘመኑን ቴክኖሎጂ በመጠቀም  በአራት በተለያዩ ቋንቋዎች(በአማርኛበትግርኛበኦሮምኛ እና በእንግሊዝኛ)  ላለፉት ዓመታት ወጥተዋል፡፡ እነዚህ ትምህርቶች ጸሐፊው በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ የኢንተርኔት አቅርቦት ላላቸው ምዕመናኖች በተቻለ መጠን ለማድረስ ሞክሯል፡፡ ነገር ግን እነዚኽን መንፈሳውያን ጽሑፎች በዓቅም ማነስ ምክንያት ቴክኖሎጂውን መጠቀም ላልቻሉ  ምእመናን ሊዳረሱ አልቻሉም፡፡

Tuesday, July 22, 2014

“ኦርቶዶክስን መሳደብ ማለት እናቴን እንደመሳደብ እቆጥረዋለሁ” አርቲስት ጥላሁን ጉግሳ


(አንድ አድርገን ሐምሌ 15 2006 ዓ.ም)፡- ከዓመታት በፊት በተሰራ አንድ ድራማ ላይ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነትን ፤ የእምነቱን አባቶችና ፤ ቤተ ክርስቲያኒቱ ያከበረቻቸው ጻድቃን ሰማዕታት ላይ የሚሳለቅ ድራማ በመስራት ለሕዝብ አቅርቧል በማለት ስሙ የሚነሳው የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ የሆነው አርቲስት ጥላሁን ጉግሳ እና ድራማው ላይ የተሳተፉ የሙያ ባልደረቦቹ በምዕመናን ዘንድ በተፈቀደ መድረክ ቤተክርስቲያኒቱን የማይመጥን ፤ ከስድብ ባለፈም አባቶች ላይ የሚያላግጥ ድራማ ነው በማለት ሰዎች ቅሬታቸውን ሲያሰሙ እንደነበር ይታወቃል፡፡(የድራማውን አንዱን ክፍል ይመልከቱ )፡