- ፍርድ ቤቱ ለእያንዳንዳቸው 6 ወር ፈርዶባቸዋል፡፡
- መንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ጀርባ የመሸጉት ቡድኖችን ይወቋቸው፡፡
(አንድ አድርገን የካቲት 13 2004 ዓ.ም)፡- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
ሃይማኖትን የሚያንቋሽሽና የሚያስተሃቅር ወንጀል ፈጽመዋል ወይም የወንጀል መቅጫ ህጉ ቁጥር 32/1ሀ ና 492/ሀ ላይ የተመለከተውን
የህግ ድንጋጌ ተላልፈዋል የተባሉ ተከሳሾች በእስራት ተቀጡ፡፡
ዐቃቢ ሕግ በመሰረተው ክስ ዲያቆን ሀብቴ ተፈራ እና ዲያቆን ጓዴ ሳህሉ የሚል
የመታወቂያ ስም ያላቸው ተከሳሾች የኦርቶዶክስ ተዋህዶን ሃይማኖት የሚያቃልል ጽሁፍ የያዘ ፓምፕሌት ይዘው ከአዲስ አበባ ተነስተው
ወደ ደብረ ታቦት ከተማ በመሄድ ባሰራጩት ጽሁፍ “እንደ እንቧይ ካብ በገዛ ራሱ
የፈራረሰው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የተሰኝው እምነት ከንቱ መዋቅር ነው ፤ እሁድ እንደ ማንኛውም የስራ ቀን ነው
፤ ቤተክርስቲያንን የሚመሩ ጳጳሳት ዝሙታን ናቸው…” የሚሉ እና የመሳሰሉት ጽሁፎች በየቦታው ሲበትኑ እንደነበርና ይህም በሰውና
በሰነድ ማስረጃ ከበቂ በላይ ተረጋግጧ ተብሏል፡፡