Saturday, January 25, 2014

ጥር 18 የቅዱስ ጊዮርጊስ ዝርዎተ አጽሙ


ቅዱስ ጊዮርጊስ ብሩክታይትን ከድራጎን ያዳነበት ስፍራ ፤ ቤሩት

(አንድ አድርገን ጥር 17 2006 ዓ.ም)፡- ከሃዲ ንጉስ ዱድያኖስ ግንድ አምጥተው ቅዱስ ጊዮርጊስን በግንዱ ላይ እንዲቸነክሩት አዘዘ  ፤በላዩም ላይ ሰም አፍስሰው እሳት እንዲያነዱበት አደረገ ከዚህም በኃላ እንደመጭመቂያ ሆኖ ከተሰራ የስቃይ መሳሪያ ላይ አወጡት ሰውነቱን እንዲሰነጥቁት እንዲጨምቁት አዘዘ ፤ አንጀቱ ሁሉ ወጥቶ ከምድር ላይ እስኪዘረገፍ ድረስ እንዲሁ አደረጉበት ነፍሱ ከስጋው ተለየች የሰማእቱን ሰጋ አቃጠሉት ፈጩት አመድም ሆነ ፤ በቀፎ አድርገው ይድራስ ወደሚባል ተራራ ላይ በነፋስ ዘሩትደብረ ይድራስ” ማለት ምድረ በዳ የሆነ ቦታ ነው፡፡ ወታደሮቹ የታዘዙትን ፈጽመው ተመለሱ። ያንጊዜም መብረቅ ነጎድጓድ ታላቅ ንውጽውጽታ ሆነ ምድርም ከመሰረቷ እስክትናወጽ ድረስ ከሰማይ ድምጽ ተሰማ ጌታችን መድሐኒታችን እየሱስ ክርስቶስ መላእክትን አስከትሎ በብሩ ደመና ወረደ በተራራውም ላይ ተቀመጠ አራቱን የምድር ነፋሳት የሰማእቱን ስጋ እንዲሰበሰቡ አዘዛቸው ከሞትም አስነሳው ኃይሉን አሳደረበት ባርኮትም ወደ ሰማይ አረገ ፤ ከዚህ በኃላ ቅዱስ ጊዮርጊስ እየሮጠ ወታደሮቹን ተከተላቸውወንድሞቼ ቆዩኝ ከእናንተ ጋር ልሂድ” እያለ ተጣራ ፤ የእነዚህ የወታደሮች ቁጥራቸው አራት ነበረ ስማቸው ህልቶን ፤ አግሎሲስ ፤ ሶሪስና አስፎሪስ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ይህንን ታላቅ ተአምራት አይተው አምነዋል፡፡ በኋላም በሰማእትነት አልፈዋል፡፡  ይህ የሆነው ጥር 18  ቀን ነው ይህንንም ቀን " ዝርዎተ አጽሙ " ስትል ቤተ ክርስቲያን ሰማእቱን አዘክራ ትውላለች፡፡ በስሙ በታነጹለት አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ ታቦተ ህጉ ውጥቶ በደማቁ ተከብሮ ይውላል። ደብረ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንንን የተከሉት ደጉ ንጉስ እምዬ ምኒሊክ ሲሆኑ የዚህን ታላቅ ደብር መሰረቱን ሲጥሉ የቅዱስ ጊዮርጊስ መቃብር ከሚገኝበት ቦታ አፈሩን በመርከብ አጓጉዘው በበቅሎ በፈረስ አስጭነው  የቤተክርስቲያኑን መሰረት አድርገውታል፡፡

Friday, January 24, 2014

አንጎለላ ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን የዝርፊያ ሙከራ ተካሄደባት

(አንድ አድርገን ጥር 15 2006 ዓ.ም)፡- ከአዲስ አበባ በስተ ሰሜን አቅጣጫ ከደብረ ብርሀን ወደ ጁሁር መስመር 12 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝው አንጎለላ ኪዳነ ምህርተ ቤተ ክርስቲያን ጥር 11 ቀን 2006 ዓ.ም ዕለተ እሁድ ለሊት ለጥር 12 አጥቢያ የዝርፊያ ሙከራ መደረጉን ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ከሦስት ዓመት በፊት ቤተ ክርስቲያኒቱ ከፍተኛ ዝርፊያ የተከናወነባት ሲሆን በዝርፊያውም ውስጥ አዋቂ ካህናት እና ደብረ ብርሃን አካባቢ የሚገኙ የተደራጁ ባለሃብቶች መሳተፋቸው ይታወቃል፡፡ የአሁኑ ዝርፊያ ለማድረግ የተሞከረው በካህናት በር በኩል ሲሆን የካህናት በር የመግቢያው ቁልፍ በብረት መጋዝ ገዝግዘው ቆርጠው ወደ ውስጥ ከገቡ በኋላ እጅግ በርካታ ቅርስ የሚገኝበትን የመቅደሱን በር ሰብሮ ለመግባት ከፍተኛ ድብደባ አድርገው ሲያበቁ በሩ አልከፈት በማለቱ በቦታው የሚገኙትን ሁለት ሙዳይ ምፅዋት ተሸክመው በመውሰድ ውስጥ ያለውን ገንዘብ ወስደው ሲያበቁ ሙዳይ ምጽዋቱን ጫካ ጥለውት ዘራፊዎቹ ከአካባቢው ተሰውረዋል፡፡ ቅርስ ዘርፎ በመሸጥ በማኅበረሰቡ የሚጠረጠሩት የደብረ ብርሃን አካባቢ ባለሃብቶች እንደ ከዚ ቀደሙ በአሁኑ ላይ ይሳተፉ አይሳተፉ የተገኝ መረጃ ባይኖርም ፖሊስ ጉዳዩን እያጣራው እንደሚገኝ የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

ፖሊስ ይህን ዝርፊያ ሊያደርጉ ይችላሉ ወይም ሊተባበሩ ይችላሉ ያላቸውን የውስጥ ካህናት ቃለ መጠይቅ በማድረግ አንዳንድ መረጃዎችን የሰበሰበ ሲሆን ከዚህ በማለፍ በጥርጣሬ የተያዘ ማንም ሰው አለመኖሩን ለማወቅ ችለናል፡፡ አንጎለላ ኪዳነምህርተ ቤተክርስቲያን ውስጧ ከሚገኝው በብር የማይገመቱ በርካታ ቅርሶች በተጨማሪ ቤተክርስቲያኒቱ አጼ ምኒሊክ የሥላሴን ልጅነት ያገኙባት (ክርስትና የተነሱባት) ቤተ ክርስቲያን መሆኗ ይታወቃል፡፡

በተያያዘ ዜና ጥር 10 ቀን 2006 ዓ.ም መናፍቃን እንደ አሸዋ በሚበዙባት በሆሳህና ከተማ 30 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝው የቡሻሻ በዓታ ለማርያም ገዳም ታቦተ ሕጉ ወደ ባሕረ ጥምቀት ከወረደ በኋላ ምክንያቱ እስከ አሁን ባልታወቀ እሳት ሙሉ በሙሉ መውደሟን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ነገስ ተጨማሪ አብያተ ክርስቲያናት ላለመቃጠላቸው ምን ዋስትና አለን… ?
እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን ይጠብቅልን

Monday, January 13, 2014

የአ/አበባ ሀ/ስብከት የመዋቅርና አሠራር ለውጥ ተቃዋሚዎች ገዳማቱንና አድባራቱን አይወክሉም

  •  ‹‹ሓላፊነትና ተጠያቂነት ያለበት አስተዳደር በቤተ ክርስቲያን ለመዘርጋት የተረቀቀው ሕግ ወደ ኋላ አይመለስም፤ መሥመሩን አይለቅም›› /ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ/

(አዲስ አድማስ ) ፡- በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ /ስብከት ለመዋቅርና አሠራር ለውጥ በባለሞያ ያካሔደውን የአደረጃጀትና የአሠራር ጥናት እንቃወማለን የሚሉ ውስን አስተዳዳሪዎችና ጸሐፊዎች አይወክሉንም ሲሉ የሀገረ ስብከቱ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ጸሐፊዎች፣ የሰበካ ጉባኤያት ምክትል ሊቃነ መናብርት፣ ልዩ ልዩ አገልጋዮችና ምእመናን ለፓትርያርክ አቡነ ማትያስ አስታወቁ፡፡ ለዘመናት የቆየው የቤተ ክርስቲያን መዋቅርና የሥራ ሒደት ከነበረው ተስፋፍቶ፣ የወቅቱን አሠራርና ሥልጣኔ የዋጀ ኾኖ በቅ/ሲኖዶስ ውሳኔና በፓትርያርኩ መልካም ፈቃድ በባለሞያዎች መዘጋጀቱንና ረቂቁ ወደ ታች ለግምገማ ወርዶ እንደተወያዩበት አስተዳዳሪዎቹና አገልጋዮቹ ጠቅሰዋል፡፡

Sunday, January 12, 2014

ሊጎበኙ የሚገባቸው መካነ ድሮች

  •    “ዘመኑ ባፈራው ቴክኖሎጂ ተጠቅመን ያዘኑትን እናጽናናቸው፤ የደከሙትን እናበርታቸው፤በአፍአ ላሉትም እንመስክርላቸው፡፡” መቅረዝ  ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

(አንድ አድርገን ጥር 3 2006 ዓ.ም)፡- ከጥቂት ዓመታት በፊት በተለያዩ ሀገራት ለሚገኙ የቤተክርስቲያን ልጆች ከመረጃ ምጭነት በተጨማሪ ለመማሪያነት እያገለገለ የሚገኝው የዘመናችን የቴክኖሎጂ ፍሬ ድረ-ገጽ ነው፡፡ ቀድሞ እንደ ደጀ-ሰላም  የመረጃ ሰሌዳ ፤ እንደ ቤተ-ደጀኔ የመማሪያ አውደ ምህረት ፤ እንደተዋሕዶሚዲያ የመዝሙር እና የስብከት ቋት እና  እንደ ስንክሳር  ያሉ መካነ ድሮች ነገረ ቅዱሳን የሚለጠፉበትና ለምዕመናን በቀላሉ የሚደርስበት ወቅት ነበር፡፡ በጊዜውም በርካቶች የመካነ ድሮቹ አባላት በመሆን ዜና የሚፈልገው የዜና ገጾችን ሲዳስስ ወንጌል ፤ ስርአተ ቤተክርስቲያን ፤ ነገረ ማርያም እና ነገረ ቅዱሳን በማንበብ ውስጡን በሃይማኖት ትምህርት ማነጽ የሚፈልገውም እንደ ፍላጎቱ መካነ ድሮችን ሲጠቀምባቸው ነበር፡፡ አሁን አሁን ግን ቀድሞ የተከፈቱት በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት የመዘጋት እጣ ፋንታ በራቸው ላይ ሲቆም ሌሎቹ ደግሞ የመደንዘዝ እና ወደፊት ያለመቀጠል ነገር ይታይባቸዋል፡፡

Tuesday, January 7, 2014

የአራቱን ኃያላን አባቶችን ታሪክና ተጋድሎ በአንድ መጽሐፍ

ተጻፈ ፡ በፍቅር ለይኩን
 

  • ‹‹በምስክርነት ካልጻፍንና ካልተናገርን የሚመጣው ትውልድ በምን ያውቃል ትውልድ ያውቅ ዘንድ ጥቂት እንጽፋለን፡፡ እኛማ እንሞታለን፣ እንጣላለንም፡፡›› (ከአራቱ ኃያላን መጽሐፍ የተወሰደ)

ጥንታዊውንና የመካከለኛው ዘመን የኢትዮጵያን ታሪክ ለማጥናትና በወጉ ለመሰነድ ካሉብንና ከሚጠቀሱ ችግሮች መካከል የመረጃ እጥረትና ክፍተት ዋንኛውና ተጠቃሹ ነው፡፡ በዘመናችንም ቢሆን ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ ሲነገርም ሆነ ሲጻፍ ‹‹የትኛዋ ኢትዮጵያ›› ወደሚል ክርክርና ማብቂያ የሌለው ወደሚመስል ሙግት ወይም እሰጥ አገባ እያስገባን ያለው በከፊልም ቢሆን  ስለትናንትና ያለን መረጃ የሳሳና እንዲያም ሲል ደግሞ እንደ ለማኝ እህል የተደበላለቀ የመሆኑ ጉዳይ ይመስለኛል፡፡

Saturday, January 4, 2014

በአዲስ አበባ የወንድ የጎዳና ሕጻናት ላይ የሚደርሰው የወሲብ ጥቃት አስመልከቶ የተደረገ ጥናት


  • በጥናቱ ላይ 35 መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተጨማሪ ቁልፍ የመረጃ ምንጮች ቃለ መጠይቅ ተደርጎላቸዋል፡፡
  • ጥቃት የደረሰባቸው አካላት ፍትህ እንዳያገኙ የምርመራው ሂደት ውጤታማ እንዳይሆን የከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ተጽህኖም አለበት ተብሏል፡፡
  • አንድ የፖሊስ መኮንን ባልደረባ በቃል እንደተናገረው “ በጉዳዩ ጥቂት ደረጃ ላይ እንደደረስክ ርቀህ እንዳትሄድ በአንዳንድ ሃላፊዎች ትከለከላለህ፡፡ በተወሰነ ደረጃ በኋላም ክትትል እንድታቆም ትታዘዛለህ፡፡”
  • “ከፍተኛ የመንግሥት አካላትን ለውይይት በምንጋብዝባቸው ጊዜ በጉዳዩ ላይ መነጋገርን የሚጠሉ ሃላፊዎችና ህግ አውጪዎች አጋጥመውናል፡፡”
  • ቁልፍ የመረጃ ምንጮች በወንዶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች ጥልቀት በአስፈሪ ሁኔታ በከተማዋ እየተስፋፋ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡
  • 25 በመቶ ያህል የወሲብ ጥቃት ሰለባ የጎዳና ወንድ ሕጻናት በአጥቂነት ተሰልፈዋል፡፡ ይህም የሚያሳየው ህጻናቱ በድርጊቱ ተሳታፊ እየሆኑ እንደመጡ ነው፡፡
  • በህብረተሰቡ ዘንድ የችግሩ ስፋት አይታወቅም፡፡ ለአቅመ አዳም ያልደረሱ በርካታ ሕጻናት የወሲብ ጥቃት እየደረሰባቸው ነው፡፡ ችግሩ በአስከፊ ደረጃ ላይ ነው ያለው፡፡ መገናኛ ብዙሀን ድርጊቱን ለማስቆም የራሳቸው ድርሻ እየተወጡ አይደለም፡፡

(አንድ አድርገን ታህሳሥ 27 2006 ዓ.ም)፡- ከ2 ዓመት በፊት አዲስ አበባ የመጀመሪያውን የግብረ ሰዶም ስብሰባ ስታስተናግድ በርካቶች ድምጻቸውን በግልጽ በማሰማት ከፍተኛ ተቃውሟቸውን መግለጻቸው ይታወቃል ፡፡ የተቃውሞ ድምጹ ስብሰባው ከመደረግ ባይከለክለው እንኳ ፤ በወቅቱ ወጣቱ ብቻ ሳይሆን የሃይማኖት አባቶች ተቃዎሟቸውን ለመግለጽ የተሰበሰቡበት የጊዮን ሆቴሉ ስብሰባ በወቅቱ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የአሁኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም አማካኝነት አቋማቸውን እንዳይገልጹ የተደረገበት ድራማዊ ትዕይንት መከናወኑ ትዝ ይለናል ፡፡ የግብረ ሰዶማውያን ስብሰባ ይካሄድበታል የተባለው ካሳንቺስ አካባቢ የሚገኝው አንድ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል ፊት ለፊት በአካል ለመቃወም የወጡት ጥቂት ወጣቶች በፌደራል ፖሊስ ተይዘው ወደ ማረፊያ እንደወረዱ እና ከስብሰባው መጠናቀቅ በኋላ ከእስር እንደተፈቱም የምናስታውሰው የወቅቱ ትኩስ አጀንዳም ነበር ፡፡ ስብሰባውን ያስተናገድው  ኢንተርናሽናል ሆቴልም አይኔን ግንባር ያድርገው “ግብረሰዶማውያን በሆቴሌ እልተሰበሰቡም” በማለት እንደሸመጠጠም የሚታወቅ ነገር ነው ፡፡ ጊዜው አልፎ ነገሮች ወደ ቀድሞ ሁኔታው ከተመለሱም በኋላ መንግሥት ሃገሪቱ ውስጥ ያሉትን የሃይማኖት አባቶች በአፍሪካ ሕብረት መሰብሰቢያ አዳራሽ በመሰብሰብ ይህን ጸያፍ ድርጊት ከረፈደም እንዲኮንኑና እንደማይቀበሉት መግለጫ እንዲሰጡም ማድረጉ ይታወሳል፡፡