Wednesday, September 30, 2015

የ‹‹ባህታዊው››ን አንዷን ዘለላ ጸጉር በ50 ብር የገዛ ሕዝብ የ‹‹መምህር›› ግርማን በስንት ይገዛው ይሆን…?


ድጋሚ የቀረበ
አንድ አድርገን መስከረም 2 2006 ዓ.ም)፤-


የልዑል እግዚአብሔር ቸርነትና አዳኝነት ከሚገለጥባቸው ምክንያቶች ወይም መንገዶች አንዱ ጠበል ነው፡፡ በገዳማትና አድባራት ቅጽር፣ በቅጽሩ ዙርያና በአካባቢው ሰበካዎች ባሉ የጠበል ቦታዎች በፍጹም እምነት የሚቀርቡ ምእመናን በጠበል እየተጠመቁ ፈውስ ያገኛሉ፤ የእግዚአብሔር ደገኛ ተኣምራት እየተገለጸ ምሕረቱ የተደረገላቸው ሁሉ በየጊዜው ድንቅ ሥራውን እየመሰከሩ ይገኛሉ፡፡


በሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን ማጥመቅ የሚችለው የቅስና ሥልጣነ ክህነት ያለው አባት ብቻ ነው፡፡ ቅስና የሌለው ሰው አያጠምቅም፤ አያናዝዝም፤ አይባርክም /ፍት....አን.3 .21/ ቅዱሱን ቅባት መቀባት የሚችለው የክህነት ሥልጣን ያለው ብቻ ነው፡፡ /ያዕ.5÷14/ ሀብተ መንፈስ ቅዱስ በገንዘብ አይሸጥምና አጥማቂው ካህን መማለጃ መቀበል አይገባውም፡፡ /....አን.7/ 

Sunday, September 20, 2015

ጠቅላይ ቤተ ክህነት: በአራዳ ጊዮርጊስ የሕንፃዎች ግንባታ በጀት ላይ ጥያቄዎች አነሣ


  •   መመሪያያልተሰጠበትየደብሩየሚሊዮንብሮችየበጀትጥያቄእንዲዘገይአዟል 
  •  የሀገረ ስብከቱን ሥራ አስኪያጅና ምክትላቸውን እያወዛገበ ነው


  (Addis Admass ) :-  
የአራዳው መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደብር፣ እያሠራው የሚገኘው የሁለገብ ሕንፃ ግንባታ፣ ተደርጎለታል ባለው የዲዛይን ማሻሻያ ሳቢያ በልዩነት የሚያስፈልገው ከመቶ ሚሊዮን ብር በላይ ወጪና ከባለሀብቶች ጋር በመተባበር ለማስገንባት ያቀዳቸው የሌሎች ሁለት ሕንፃዎች ግንባታና በጀት እንዲጸድቁለት ያቀረባቸው ጥያቄዎች፣ ለፓትርያርኩ ቀርበው መመሪያ ያልተሰጠባቸው በመሆናቸውበአሉበት ሁኔታ እንዲቆዩየመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት /ቤት አዘዘ፡፡

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳደር ጉባኤ፣ በደብሩ ግንባታዎችና የበጀት ይጸደቅልኝ ጥያቄዎቹ ላይ ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር መጨረሻ ያሳለፋቸው ውሳኔዎች ለአፈጻጸም ወደ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ /ቤቱ ሳይላኩለት የቆዩበት ምክንያት እንዲብራራለትም ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ከትላንት በስቲያ ለሀገረ ስብከቱ በጻፈው ደብዳቤ ጠይቋል፡፡

Friday, September 18, 2015

ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሕግ የሚጠየቁ ሙሰኛ ኃላፊዎች በዝርዝር እንዲቀርቡለት አዘዘ



-    የተቋቋመውን ኮሚቴ ለመደለልና ለማስፈራራት ተጠርጣሪዎቹ እየሠሩ ነው
 በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት፣ ቤተ ክርስቲያኒቱን ተጠቃሚ በማያደርጉ የመሬት እና የገቢ ማስገኛ ተቋማት የኪራይ ውሎች፣ የተጧጧፈ ዘረፋና ምዝበራ መፈጸሙን በጥናት ያረጋገጠው የጠቅላይ ቤተ ክህነት /ቤት÷ በጥምርና በተናጠል በሕግ ተጠያቂ የሚኾኑ የሥራ ሓላፊዎችና ሠራተኞች በስም ዝርዝር ተለይተው እንዲቀርቡለት ለአጥኚ ኮሚቴው ትእዛዝ ሰጠ፤ በመሬት፣ በሕንጻዎች፣ በሱቆች፣ በመቃብር ቦታዎች፣ በመኪና ሽልማትና በመሳሰሉት የልማት ሥራዎች ዙሪያ በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው ስለሚገቡ ነጥቦች፣ ለሀገረ ስብከቱ ጥብቅ መመሪያም አስተላልፏል።